ያባቴ ዘር ድሩ
የእናቴ ዘር ማጉ
በሸማኔው ታሪክ
እኔን ሲደረጉ
ድርን የኔ ብዬ
ማግን እንዴት ልተው
እኔነት ሸማዬን
እየመሠረተው?
ማግን የኔ ብዬስ
ድርን እንዴት ልጥላ?
በርሱም አይደለ ወይ
የሆንኩት ነጠላ!
ያለማግ ሸማ አልሆን ያለድርም ኩታ
ለድርም ለማግም አለኝ ከበሬታ
ድር ነኝ በይ! ማግ ነኝ በይ!
የሚለው ጉተታ
በሸማው ልቤ ውስጥ አይኖረውም ቦታ።
by Ze’ab Alube
የእናንተስ ?
