ብሔርንም በተመለከተ ያልተዛመድኩት ብሔር የለኝም!!..የኔ ቤተሰብ ውስጥ ሁሌም ትንሿን ኢትዮጵያዬን ነው የማየው። ለዚህ ነው እኔ እራሴን አንድ ጥግ ውስጥ ላስቀምጥሽ ብላት ማንነቴ የማትፈቅድልኝ!!..ሁሌም” #እኔ_የማውቀው_መጀመሪያ_ሰው_መሆኔን_ሲቀጥል_ ኢትዮጵያዊ_መሆኔን_ብቻ_ነው!!” የምለው፤ ይህንን ሕብር ማንነቴን ጠቅልሎ የሚገልጽልኝ #ሰውነት እና #ኢትዮጵያዊነት ብቻ ስለሆነ ነው!!!
አምላካችን ሀገራችንን በምህረቱ ይጎብኝልን!!